የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር በኢራን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ለጊዜው ማቆማቸውን አስታወቁ
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ በኢራን ላይ የሚያካሂዱትን ጥቃት “ለአሁን” መግታታቸውን ባደረጉት ንግግር አስታወቁ።
በቴሌቪዥን በተላለፈው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር የእስራኤል ሠራዊት በወሰዳቸው እርምጃዎች ኢራን እና ሄዝቦላህ ከመቼውም ጊዜ በላይ መዳከማቸውን አመልክተዋል።
ኢራን እሁድ ሌሊት በእስራኤል ላይ የፈጸመችውን የሚሳዔል ጥቃት ተከትሎ በአጸፋው የቴህራንን ወታደራዊ ዒላማዎች መምታቷ ተዘግቧል።
ይህ የእስራኤል ጥቃት በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጠያቂነት እንደሚቆም ከተነገረ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባረድጉት ንግግር ላይ ጥቃታቸውን ለጊዜው እንዲቆም ማድረጋቸውን ነገር ግን ውጊያው ገና አለማብቃቱን ገልጸዋል።
ለኢራን ጥቃት ምላሽ በመሰጠቱ "አሁን ተኩሱ ተገትቷል” ሲሉ ኔታኒያሁ ተናግረዋል።
ነገር ግን “ኢራን በድጋሚ ስህተት በመፈጸም ጥቃት የምትፈጽም ከሆነ በከፍተኛ ኃይል ምላሽ እንሰጣለን” ሲሉ ያስጠነቀቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እስራኤል እራሷን ለመከላከል ሙሉ መብት ያላት ሲሆን፣ ይህንንም አስፈላጊ አስከሆነ ድረስ ሙሉ ለሙሉ እንጠቀምበታለን” ብለዋል።
ኔታኒያሁ በተጨማሪም በኢራን እና በእስራኤል መካከል የጥቃት መመላለስ መከሰቱን ተከትሎ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አረጋግጠዋል።